መንበርና እርካብ
ሐ ተ ታ ግ ም ገ ማ መንበር ና እርካብ የአገር መሪዎች ሥልጣን ላይ ከመውጣቸው በፊት ወይም ከወረዱ በኋላ የራእያቸውንና የታሪካቸውን ሰነድ ይጽፋሉ፣ ያጽፋሉ። ሂትለር “ ማይን ካምፍ ” ( “ ትግሌ ” የተሰኘ ማኒፌስቶ ) ፤ ባራክ ኦባማ ፕሬዚደንት ለመሆን ከመወዳደራቸው ከዓመት ተኲል አስቀድሞ ( በ 1998 ዓ . ም .) “ ዘ ኦዳሲቲ ኦፍ ሆፕ ” ን አሳትመዋል። ዶ / ር ዐቢይ አሕመድ የጠ / ሚንስትርነቱን እርካብ ረግጠው መንበሩን ከመቆናጠጣቸው ከዓመት ተኲል በፊት ( በ 2009 ዓ . ም .) “ እርካብና መንበር ” ን “ ዲራአዝ ” በሚል የብዕር ስም አሳትመዋል። እርካብ የሚያገለግለው ለመወጣጫ ብቻ አይደለም፤ ላደለው ለመውረጃም ነው። ከቴዎድሮስ እስከ መለስ፣ ሞት ወይም እርካብ ተበጥሶ መሪዎቻችንን አንድባንድ አሰናብቶብናል ! አፄ ኃ / ሥ ከ 1923 ዓ . ም . እስከ 1966 ዓ . ም . ድረስ ነግሠው፣ ከዙፋን ሊወርዱ ዓመት ሲቀራቸው ( በ 1965 ዓ . ም .) “ ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ ” ን አሳትመዋል። የርእሱን ቅደም ተከተል ብንመለከት፣ “ ሕይወቴ ” ከ “ ኢትዮጵያ እርምጃ ” ይቀድማል፤ ወይም “ ሕይወቴ ” እና “ የኢትዮጵያ እርምጃ ” አይነጣጠሉም የሚል ይመስላል። የንግሣቸውም ዘመን ባልተፈጸመ ትንቢታዊ የተስፋ ቃል ተቋጭቷል፦ “ ህግ ለሰው ሁሉ የበለጠ የሚጠቅም መሆኑን ማንም አይስተውም። መከበርም መጠቀምም የሚገኙት ከህግ መተካከል የተነሣ ነው። መዋረድም መጎዳትም የሚመጡት ከህግ መጓደል ...