እንደሚወራው አይደለም
እንደሚወራው አይደለም የዛሬ ሁለት ዓመት ቢል ጌትስ ኢትዮጵያን በጎበኘበት ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የተነሡት ፎቶ ነው። ከበስተ ኋላቸው የሚታየው የስንዴ እርሻ ነው። ቢል ጌትስ በጣም ሃብታም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ በእርዳታ ስም የዓለም የሥልጣን ማዕከሎችን ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ሰው ነው። በጎ አድራጊ አይደለም ለማለት አይደለም። በጎ በማድረግ ውስጥ ግን ዓለምን በአምሳሉ መጠፍጠፍ ይዟል። አፍሪካውያን በብዛት ስለሚዋለዱ፣ ፈልሰው የአውሮጳን ደም እንዳይከልሱ ያለ ግለ ሰብ ነው። "አላስፈላጊ" ውርጃና ፅንስን መቆለፍን ይደግፋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማድረግ የተቻለው ሰው ነው። የእኛው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ያለ ቢል ጌትስ እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት ዲሬክተር መሆን ቀርቶ ደጁን አይረግጥም ነበር። ህንዷ ሳይንቲስት ዶ/ር ቫንዳና ሺቫ፣ ስለ ጌትስ የሚገርም አሳብ የሠነዘረችበትን ለማዳመጥ ሊንኩን እዚህ ተመልከቱ። ትንሽ ሰጥቶ ገፈፋ ነው ብላለች። ለመሆኑ ጌትስ እና ዐቢይ ማንም አጠገባቸው ሳይኖር ምን ተባብለው ይሆን? ይህን አጣርቶ የሚነግረን አለ? ዐቢይ ማጋነን ስለሚያበዙ ቃላቸውን መተማመን ከቶ አይቻልም። ጌትስ፣ በ2002 ዓም መለስ ዜናዊ ጋ መጥቶ፣ "ጂ ኤም ዖ" ስንዴ ድርቅና ረሓብ ላጠቃቸው አገሮች (እንደ ኢትዮጵያ ላሉት) ትልቅ ምርት ያስገኛል የሚል ሸቀጥ አራግፎ ነበር። 2,400 ገበሬዎች 100,000 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዝራት ጀምረው ነበር። አሳቡ ከጌትስ ነው፣ መሞከሪያው አፈሩ የኛ ነው። ዐቢይ፣ ስንዴ ከውጭ ማምጣት ትተን ውጭ አገር መላክ ጀምረናል ባሉን ወቅት፣ ስንት ሺህ ቶን ስንዴ ጂቡቲ ላይ እየተራገፈ ነበር። ያመረትነው ስንዴ ኮታው በጣም ከፍ ማለቱ እውነት ነ...