Posts

World History

Obama Factor: Ethiopians and Their Place in World History by Mitiku Adisu Important paleontological findings of the past three decades have identified Ethiopia as providing the firmest clue to human origins and to ‘conceptual thinking.’ This statement is, however, too general for our present purposes. With Barack Obama taking center stage and Abraham Lincoln’s 200th birthday approaching we may want to revisit specific contributions Ethiopians have made to world community. In an earlier post we cited that the Luo in Kenya, Southern Sudan and possibly Uganda claim Obama as one of their own; Ethiopians, on the other hand, opted to rename him Brook [blessed v. blessing] in the hope that he will be the one blessing we need to end the deception and misery being carried out in the name of democracy. But unlike Kenyans and Sudanese we already have Abe Lincoln, Alexander Pushkin, and Peter Ustinov in our list of notables. How so? Well, Abe Linco...

ምክክር ምክክር ምክር የማይሰማ ማ ይሆን?

የምክክር ኮሚሽኑ የተጠቃለሉ አጀንዳዎችን በሚቀጥለው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ተገለጸ። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም ዋና ዋና ክንውኖችና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክቶ ጷጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ፣ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርአያ (ፕሮፌሰር) የተጠቃለሉ የአጀንዳ የውሳኔ ሐሳቦች መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ተናገሩ። ይህም የሚሆነው ለተሳናባቾቹ የፓርላማ አባላት ስንብት ከመደረጉ በፊት መሆኑን ተናግረዋል። 400 አጀንዳዎች እየተደራጁ መሆኑን የገለጹት ዋና ኮሚሽነሩ፣ መንግሥት የአጀንዳ ትግበራን የሚከታተልበትን የዕቅድ ስትራቴጂ አስመልክቶ ራሱን የቻለ ምክረ ሐሳብ ለማቅረብ እየተዘጋጁ መሆናቸውን አስረድተዋል። [ሪፖርተር ጋዜጣ በፌስቡክ ገጹ፣ መስከረም 1/2019 ዓም] ኮሚሽኑ ምን ያህል ነፃ እንደ ሆነ ይታያል። የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ከሆነም ይታያል። የራሱን ሥራ ሪፖርት መንግሥት ሳንሡር ሳያደርገው በቀጥታ ለሕዝብ ማሠራጨት ይችላል? ያ ካልሆነ ኮሚሽነሩ፣ ፕሮፌሰር መስፍን አርኣያ ሥልጣኔን እለቃለሁ ብለው እንደ ነበር አንርሳ! በሌላ ሥፍራ እንዳመለከትኩት፣ የኢትዮጵያ ችግሯ እርስበርስ አለመተማመን ነው፤ መተማመንን ሳይሆን አለመተማመንን ሥራዬ ብሎ የሚዘራ አመራር መኖሩ ነው!

ሰላም በአዲሱ ዓመት

ለ2019 ዓም ዘመን መለወጫ ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የተላለፈ መልእክት ። የሚንስትሩን ቃል አንባቢ ከሕዝቡ ኑሮ ጋር እያስተያየ በጥንቃቄ ያንብብ። በያመቱ ይህን የመሰሉ የምኞት መግለጫዎችን ሰምተናል። ጥያቄው፦ ዐቢይ ሥልጣን ከያዙበት ከ2010 ዓም ጀምሮ የሕዝቡ ኑሮ ምን ያህል ተሻሻለ የሚለው ነው። እርግጥ ነው፣ አገር ማስተዳደር ቀላል አይደለም፤ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ያለች አገር። ዋነኛው ችግር አለመተማመን ነው። ዐቢይን ሕዝብ ያምናቸዋል? ዐቢይ ሕዝብ እንዳያምናቸው ድርሻቸው ምን ያህሉ ነው? አጻጻፋቸው ሁልጊዜ በ"እኛ እና በ"እነርሱ" ከፋፍሎ ነው፦ እነዚያ "ሕዝብ የከፋፈሉና የጨረሱ ..." ተብለዋል። (እኛ ግን) "አስደናቂ ታሪኮችን እየሰራን ነው።" "ፈጣሪ" ከእኛ ጋር ነው... ከእነዚያ ጋር ግን አይደለም! እውነቱ ይህ ነው፦ ብዙሓኑ ሕዝብ ይኸ ዓይነት ንግግር የተጋነነ እንደ ሆነ አውቆ እጅ እጅ ብሎታል። ከመሰልቸቱ ብዛት ልቡን ሰጥቶ አያደምጠውም። ይኸ የሕዝብ አኳኋን ለአገር መሪ ትልቅ አደጋ ቋጥሯል። አፄ ኃይለሥላሴን መንግሥቱ ኃይለማርያምን መለስ ዜናዊ አገር የከዳቸው ድንገት ባንድ ጀምበር አይደለም። ቀድሞውንም ከድቷቸው ኖሮ ጊዜ ሲፈቅድለት የሸሸገውን ልቡን ገልጦ ነው። እግዚአብሔር እግዚአብሔር የሚሉት ዐቢይ፣ ልባቸውን እንዲመክርላቸው ቢፈቅዱለት ለርሳቸውም ለአገርም በበጀ። ሌላኛው ችግር፣ ዐቢይ መስማት የማይፈልጉት እውነታ በአደባባይ እንዳይነገር ማገዳቸው ዋጋ ማስከፈሉ ነው። የተከበቡት ከታሪክ እውነት በራቀ ምኞትና፣ ሊሰሙት በሚሹት ቃላት በሚክቧቸው አድርባዮች ነው። ከላይ የጠቀስዃቸው ሦስት መሪዎችን ከሕዝብ ያራቃቸው ለውርደትና ለውድቀት የዳረጋቸው እንዲህ ዓይነቱ የሕዝብ ስሜ...

መዝሙር እና ፖለቲካ

Image
በመዝሙር ብቻ የምናውቀው ደረጀ ከበደ ወንድማችን ዘማሪ ደረጀ ከበደ በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየቱን መሠንዘር ከጀመረ ዓመት ሆኖታል። የፌስቡክ ታዳሚዎቹ፣ "ይኸ እርሱ አይደለም፣ በስሙ የሚነግዱ ግለሰቦች ናቸው" ወይም "ደረጀ እዚህ ዓይነት ውስጥ ባይጠላለፍ መልካም ነው" ወይም “ዶ/ር እንኳን የፌስቡክ ገጽህ ጓደኞች ልንሆን መድረክ ላይ ቆመህ ስታገለግል እንኳን ለማየት” ያልታደልን ነን እያሉ ነው። "እኔ ደረጀ ነኝ" ቢላቸውም፣ "በቪዲዮ ፊትህን አሳየንና፣ ድምጽህን አሰማንና እንጂ አናምንም" ብለዋል። ይኸ ሁሉ የሚያሳየው፣ ደረጀ ዓመታት ነጒደው እንኳ በሕዝብ ዘንድ ያሳደረው ፍቅር አለመደብዘዙን ነው። የእግዚአብሔር ጸጋ እውነትም አያረጅም፣ አያስረጅም! ደረጀ ከጅምሩ፣ “ፖስት የማደርጋቸው አስተያየቶችና ፅሁፎች የማይመቻችሁ ወገኖች ሰላማችሁ እንዳይደፈርስ በፍቅር ራሳችሁን ከገፁ ማግለል ትችላላችሁ” ብሏቸዋል። አባባሉ ግን ጥያቄ ያስነሳል። ለምሳሌ፣ መብትን በፍቅር ስለ መያዝ ምን ይነግረናል? መብት ዕንቅፋት ሲሆንስ? ( 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡9 ) በቀደመው ጥሪ ጸንቶ ማገልገል እንዴት ይቻላል? ( 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፤ ራእይ 2፡4፣5 ) ከስደት ዘመን ይልቅ በ “ሰላምና ነጻነት” ዘመን እነዚህን ጥያቄዎች መጠየቅ ግድ ነው። ደረጀ ፈር ቀዳጅ ነው፤ ዓይነተኛ ነው። ይህን በተለየ መንገድ የተረዳሁት ያሳተማቸውን ዘጠኝ አልበሞች በቅደም ተከተል ደርድሬ ለሰዓታት ባዳመጥኩ ጊዜ ነው። ረጅም “የክርስቲያን ጒዞ” እንደ መጓዝ ነው። ከርቀት ኮረብታን እንደ ማየት፣ አልፎ ወደ ኋላ መመልከት። ለምለም ሣር፣ ወንዝ፣ ቀጥሎ ምድረበዳ። ደስታ፣ ግራ መጋባት፤ የጠራ ሰማይ፣ የፀሐይ ሐሩር፣ ዶፍ፣ ነፋስ፣ ጠ...

የዘር ባንክ

Image
ስንዴ ጌትስ የዛሬ ሁለት ዓመት ቢል ጌትስ ኢትዮጵያን በጎበኘበት ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የተነሡት ፎቶ ነው። ከበስተ ኋላቸው የሚታየው የስንዴ እርሻ ነው። ቢል ጌትስ በጣም ሃብታም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ በእርዳታ ስም የዓለም የሥልጣን ማዕከሎችን ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ሰው ነው። በጎ አድራጊ አይደለም ለማለት አይደለም። በጎ በማድረግ ውስጥ ግን ዓለምን በአምሳሉ መጠፍጠፍ ይዟል። አፍሪካውያን በብዛት ስለሚዋለዱ፣ ፈልሰው የአውሮጳን ደም እንዳይከልሱ ያለ ግለ ሰብ ነው። "አላስፈላጊ" ውርጃና ፅንስን መቆለፍን ይደግፋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማድረግ የተቻለው ሰው ነው። የእኛው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ያለ ቢል ጌትስ እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት ዲሬክተር መሆን ቀርቶ ደጁን አይረግጥም ነበር።  ህንዷ ሳይንቲስት ዶ/ር ቫንዳና ሺቫ፣ ስለ ጌትስ የሚገርም አሳብ የሠነዘረችበትን ለማዳመጥ ሊንኩን እዚህ ተመልከቱ። ትንሽ ሰጥቶ ገፈፋ ነው ብላለች። ለመሆኑ ጌትስ እና ዐቢይ ማንም አጠገባቸው ሳይኖር ምን ተባብለው ይሆን? ይህን አጣርቶ የሚነግረን አለ? ዐቢይ ማጋነን ስለሚያበዙ ቃላቸውን መተማመን ከቶ አይቻልም።  ጌትስ፣ በ2002 ዓም መለስ ዜናዊ ጋ መጥቶ፣ "ጂ ኤም ዖ" ስንዴ ድርቅና ረሓብ ላጠቃቸው አገሮች (እንደ ኢትዮጵያ ላሉት) ትልቅ ምርት ያስገኛል የሚል ሸቀጥ አራግፎ ነበር። 2,400 ገበሬዎች 100,000 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዝራት ጀምረው ነበር። አሳቡ ከጌትስ ነው፣ መሞከሪያው አፈሩ የኛ ነው። ዐቢይ፣ ስንዴ ከውጭ ማምጣት ትተን ውጭ አገር መላክ ጀምረናል ባሉን ወቅት፣ ስንት ሺህ ቶን ስንዴ ጂቡቲ ላይ እየተራገፈ ነበር። ያመረትነው ስንዴ ኮታው በጣም ከፍ ማለቱ እውነት ነው። እንኳን...