Posts

እንደሚወራው አይደለም

Image
እንደሚወራው አይደለም የዛሬ ሁለት ዓመት ቢል ጌትስ ኢትዮጵያን በጎበኘበት ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የተነሡት ፎቶ ነው። ከበስተ ኋላቸው የሚታየው የስንዴ እርሻ ነው። ቢል ጌትስ በጣም ሃብታም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ በእርዳታ ስም የዓለም የሥልጣን ማዕከሎችን ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ሰው ነው። በጎ አድራጊ አይደለም ለማለት አይደለም። በጎ በማድረግ ውስጥ ግን ዓለምን በአምሳሉ መጠፍጠፍ ይዟል። አፍሪካውያን በብዛት ስለሚዋለዱ፣ ፈልሰው የአውሮጳን ደም እንዳይከልሱ ያለ ግለ ሰብ ነው። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማድረግ የተቻለው ሰው ነው። የእኛው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ያለ ቢል ጌትስ እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት ዲሬክተር መሆን ቀርቶ ደጁን አይረግጥም ነበር።  ህንዷ ሳይንቲስት ዶ/ር ቫንዳና ሺቫ፣ ስለ ጌትስ የሚገርም አሳብ የሠነዘረችበትን ለማዳመጥ ሊንኩን እዚህ ተመልከቱ። ትንሽ ሰጥቶ ገፈፋ ነው ብላለች። ለመሆኑ ጌትስ እና ዐቢይ ማንም አጠገባቸው ሳይኖር ምን ተባብለው ይሆን? ይህን አጣርቶ የሚነግረን አለ? ዐቢይ ማጋነን ስለሚያበዙ ቃላቸውን መተማመን ከቶ አይቻልም።  ጌትስ፣ በ2002 ዓም መለስ ዜናዊ ጋ መጥቶ፣ "ጂ ኤም ዖ" ስንዴ ድርቅና ረሓብ ላጠቃቸው አገሮች (እንደ ኢትዮጵያ ላሉት) ትልቅ ምርት ያስገኛል የሚል ሸቀጥ አራግፎ ነበር።  2,400 ገበሬዎች 100,000 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዝራት ጀምረው ነበር። አሳቡ ከጌትስ ነው፣ መሞከሪያው መሬት ከኛ ነው። ያገሬ ገበሬ ከፈለገ አፈር ይብላ።  ጌትስ፣ ሞንሳንቶ ከተባለ ድርጅት ጋር የንግድ ሽርክና አለው።  አገራችን አንድ ሃብቷ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር ባደላትና ምስኪን ገበሬዎቿ ያከማቹት የእርሻ ጥበብና ልዩ ልዩ የአዝርእት ዘ...

Ancient Origins of the Ethiopian Calendar

Image
Why Ethiopia Has Its Own Calendar: The Ancient Origins of the Ethiopian Calendar Girma A Demeke (PhD), Research & Publication Director, Institute of Semitic Studies Ethiopia will soon celebrate its New Year, marking a calendar transition distinct from the internationally adopted Gregorian system. This divergence includes both the method of calculating years and the fundamental structure of the day Specifically, from September 11/12 to 31 December, the Ethiopian calendar trails the Gregorian calendar by seven years, and by eight years from 1 January to September 10/11.  Additionally, while the Gregorian day commences at midnight, the Ethiopian day begins at dawn.  Explanations regarding the origins of these differences are often incomplete or convoluted by religious dogma, leaving the underlying mechanics poorly understood. A decade ago, we addressed this topic extensively in a book published in Amharic:  Girma A. Demeke. 2016. The Ethiopian Calendar (Text in Amhari...

አንቀላውጥ፣ ያለው ይበቃናል

Image
  አንቀላውጥ፣ ያለው ይበቃናል ክፍል አንድ ፦ እስከ 1966 ዓም ድረስ " የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር ” ኢትዮጵያ ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! ነበር። በማን ደስ ይበልሽ ? በአምላክሽ። በንጉሥሽ። አምላክሽ እና ንጉሥሽ አይነጣጠሉም፤ ሁለቱም ድል አድራጊ ናቸው። ሁለቱም አይደረስባቸውም። ንጉሥ አይከሰስም፤ ሰማይ አይታረስም። ብቻ ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ። ድህነትሽን ጉስቊልናሽን አታስቢ። ንጉሥሽ ክብርሽ ነው፤ በድህነትሽ አትፈሪ። አምላክ አለልሽ። ንጉሥ አለልሽ። በምድር ያጣሽውን በሰማይ ትካሺያለሽ። “ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ በአምላክሽ ኃይል በንጉሥሽ ተባብረዋል አርበኞችሽ አይነካም ከቶ ነጻነትሽ ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ አትፈሪም ከጠላቶችሽ ድል አድራጊው ንጉሳችን ይኑርልን ለክብራችን” ነበር። [ ግጥም፦ ዮፍታሔ ንጉሤ። ዜማ ( አርመናዊው ) ነርሲስ ናልባንዲያን ] ክፍል ሁለት ፦ ደርግ መጥቶ፦ የምን ንጉሥ ነው ? ወዲያልኝ አለ። የምን እግዚአብሔር ? ወዲያልኝ አለ። ከ 1967 ዓም እስከ 1984 ዓም የኢትዮጵያ ልጆች ባንድነት፦ " ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ቅደሚ " አልን። “ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ ፡ ቅደሚ ፣ በኅብረሰባዊነት ፡ አብቢ ፡ ለምልሚ! ቃል ፡ ኪዳን ፡ ገብተዋል ፡ ጀግኖች ፡ ልጆችሽ ፣ ወንዞች ፡ ተራሮችሽ ፣ ድንግል ፡ መሬትሽ ፣ ለኢትዮጵያ ፡ አንድነት ፡ ለነጻነትሽ ፣ መሥዋዕት ፡ ሊኾኑ ፡ ለክብር ፡ ለዝናሽ ። ተራመጂ ፡ ወደፊት ፡ በጥበብ ፡ ጎዳና ፣ ታጠቂ ፡ ለሥራ ፡ ላገር ፡ ብልጽግና” አሉ። [ ግጥም፦ አሰፋ ገብረ ማርያም ተሰማ። ዜማ፦ ዳንኤል ዮሐንስ ሐጎስ ...