አንቀላውጥ፣ ያለው ይበቃናል
አንቀላውጥ፣ ያለው ይበቃናል ክፍል አንድ ፦ እስከ 1966 ዓም ድረስ " የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር ” ኢትዮጵያ ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! ነበር። በማን ደስ ይበልሽ ? በአምላክሽ። በንጉሥሽ። አምላክሽ እና ንጉሥሽ አይነጣጠሉም፤ ሁለቱም ድል አድራጊ ናቸው። ሁለቱም አይደረስባቸውም። ንጉሥ አይከሰስም፤ ሰማይ አይታረስም። ብቻ ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ። ድህነትሽን ጉስቊልናሽን አታስቢ። ንጉሥሽ ክብርሽ ነው፤ በድህነትሽ አትፈሪ። አምላክ አለልሽ። ንጉሥ አለልሽ። በምድር ያጣሽውን በሰማይ ትካሺያለሽ። “ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ በአምላክሽ ኃይል በንጉሥሽ ተባብረዋል አርበኞችሽ አይነካም ከቶ ነጻነትሽ ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ አትፈሪም ከጠላቶችሽ ድል አድራጊው ንጉሳችን ይኑርልን ለክብራችን” ነበር። [ ግጥም፦ ዮፍታሔ ንጉሤ። ዜማ ( አርመናዊው ) ነርሲስ ናልባንዲያን ] ክፍል ሁለት ፦ ደርግ መጥቶ፦ የምን ንጉሥ ነው ? ወዲያልኝ አለ። የምን እግዚአብሔር ? ወዲያልኝ አለ። ከ 1967 ዓም እስከ 1984 ዓም የኢትዮጵያ ልጆች ባንድነት፦ " ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ቅደሚ " አልን። “ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ ፡ ቅደሚ ፣ በኅብረሰባዊነት ፡ አብቢ ፡ ለምልሚ! ቃል ፡ ኪዳን ፡ ገብተዋል ፡ ጀግኖች ፡ ልጆችሽ ፣ ወንዞች ፡ ተራሮችሽ ፣ ድንግል ፡ መሬትሽ ፣ ለኢትዮጵያ ፡ አንድነት ፡ ለነጻነትሽ ፣ መሥዋዕት ፡ ሊኾኑ ፡ ለክብር ፡ ለዝናሽ ። ተራመጂ ፡ ወደፊት ፡ በጥበብ ፡ ጎዳና ፣ ታጠቂ ፡ ለሥራ ፡ ላገር ፡ ብልጽግና” አሉ። [ ግጥም፦ አሰፋ ገብረ ማርያም ተሰማ። ዜማ፦ ዳንኤል ዮሐንስ ሐጎስ ...