Posts

ምክክር ምክክር ምክር የማይሰማ ማ ይሆን?

የምክክር ኮሚሽኑ የተጠቃለሉ አጀንዳዎችን በሚቀጥለው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ተገለጸ። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም ዋና ዋና ክንውኖችና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክቶ ጷጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ፣ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርአያ (ፕሮፌሰር) የተጠቃለሉ የአጀንዳ የውሳኔ ሐሳቦች መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ተናገሩ። ይህም የሚሆነው ለተሳናባቾቹ የፓርላማ አባላት ስንብት ከመደረጉ በፊት መሆኑን ተናግረዋል። 400 አጀንዳዎች እየተደራጁ መሆኑን የገለጹት ዋና ኮሚሽነሩ፣ መንግሥት የአጀንዳ ትግበራን የሚከታተልበትን የዕቅድ ስትራቴጂ አስመልክቶ ራሱን የቻለ ምክረ ሐሳብ ለማቅረብ እየተዘጋጁ መሆናቸውን አስረድተዋል። [ሪፖርተር ጋዜጣ በፌስቡክ ገጹ፣ መስከረም 1/2019 ዓም] ኮሚሽኑ ምን ያህል ነፃ እንደ ሆነ ይታያል። የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ከሆነም ይታያል። የራሱን ሥራ ሪፖርት መንግሥት ሳንሡር ሳያደርገው በቀጥታ ለሕዝብ ማሠራጨት ይችላል? ያ ካልሆነ ኮሚሽነሩ፣ ፕሮፌሰር መስፍን አርኣያ ሥልጣኔን እለቃለሁ ብለው እንደ ነበር አንርሳ! በሌላ ሥፍራ እንዳመለከትኩት፣ የኢትዮጵያ ችግሯ እርስበርስ አለመተማመን ነው፤ መተማመንን ሳይሆን አለመተማመንን ሥራዬ ብሎ የሚዘራ አመራር መኖሩ ነው!

በአዲሱ ዓመት እውነት የሚናገሩ እግዚአብሔር የሚፈሩ ሕዝብ የሚያከብሩ መሪዎች ያስነሳልን

ለ2019 ዓም ዘመን መለወጫ ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የተላለፈ መልእክት ። የሚንስትሩን ቃል አንባቢ ከሕዝቡ ኑሮ ጋር እያስተያየ በጥንቃቄ ያንብብ። በያመቱ ይህን የመሰሉ የምኞት መግለጫዎችን ሰምተናል። ጥያቄው፦ ዐቢይ ሥልጣን ከያዙበት ከ2010 ዓም ጀምሮ የሕዝቡ ኑሮ ምን ያህል ተሻሻለ የሚለው ነው። እርግጥ ነው፣ አገር ማስተዳደር ቀላል አይደለም፤ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ያለች አገር። ዋነኛው ችግር አለመተማመን ነው። ዐቢይን ሕዝብ ያምናቸዋል? ዐቢይ ሕዝብ እንዳያምናቸው ድርሻቸው ምን ያህሉ ነው? አጻጻፋቸው ሁልጊዜ በ"እኛ እና በ"እነርሱ" ከፋፍሎ ነው፦ እነዚያ "ሕዝብ የከፋፈሉና የጨረሱ ..." ተብለዋል። (እኛ ግን) "አስደናቂ ታሪኮችን እየሰራን ነው።" "ፈጣሪ" ከእኛ ጋር ነው... ከእነዚያ ጋር ግን አይደለም! እውነቱ ይህ ነው፦ ብዙሓኑ ሕዝብ ይኸ ዓይነት ንግግር የተጋነነ እንደ ሆነ አውቆ እጅ እጅ ብሎታል። ከመሰልቸቱ ብዛት ልቡን ሰጥቶ አያደምጠውም። ይኸ የሕዝብ አኳኋን ለአገር መሪ ትልቅ አደጋ ቋጥሯል። አፄ ኃይለሥላሴን መንግሥቱ ኃይለማርያምን መለስ ዜናዊ አገር የከዳቸው ድንገት ባንድ ጀምበር አይደለም። ቀድሞውንም ከድቷቸው ኖሮ ጊዜ ሲፈቅድለት የሸሸገውን ልቡን ገልጦ ነው። እግዚአብሔር እግዚአብሔር የሚሉት ዐቢይ፣ ልባቸውን እንዲመክርላቸው ቢፈቅዱለት ለርሳቸውም ለአገርም በበጀ። ሌላኛው ችግር፣ ዐቢይ መስማት የማይፈልጉት እውነታ በአደባባይ እንዳይነገር ማገዳቸው ዋጋ ማስከፈሉ ነው። የተከበቡት ከታሪክ እውነት በራቀ ምኞትና፣ ሊሰሙት በሚሹት ቃላት በሚክቧቸው አድርባዮች ነው። ከላይ የጠቀስዃቸው ሦስት መሪዎችን ከሕዝብ ያራቃቸው ለውርደትና ለውድቀት የዳረጋቸው እንዲህ ዓይነቱ የሕዝብ ስሜ...

በመዝሙር ብቻ የምናውቀው ደረጀ ከበደ

Image
በመዝሙር ብቻ የምናውቀው ደረጀ ከበደ ወንድማችን ዘማሪ ደረጀ ከበደ በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየቱን መሠንዘር ከጀመረ ዓመት ሆኖታል። የፌስቡክ ታዳሚዎቹ፣ "ይኸ እርሱ አይደለም፣ በስሙ የሚነግዱ ግለሰቦች ናቸው" ወይም "ደረጀ እዚህ ዓይነት ውስጥ ባይጠላለፍ መልካም ነው" ወይም “ዶ/ር እንኳን የፌስቡክ ገጽህ ጓደኞች ልንሆን መድረክ ላይ ቆመህ ስታገለግል እንኳን ለማየት” ያልታደልን ነን እያሉ ነው። "እኔ ደረጀ ነኝ" ቢላቸውም፣ "በቪዲዮ ፊትህን አሳየንና፣ ድምጽህን አሰማንና እንጂ አናምንም" ብለዋል። ይኸ ሁሉ የሚያሳየው፣ ደረጀ ዓመታት ነጒደው እንኳ በሕዝብ ዘንድ ያሳደረው ፍቅር አለመደብዘዙን ነው። የእግዚአብሔር ጸጋ እውነትም አያረጅም፣ አያስረጅም! ደረጀ ከጅምሩ፣ “ፖስት የማደርጋቸው አስተያየቶችና ፅሁፎች የማይመቻችሁ ወገኖች ሰላማችሁ እንዳይደፈርስ በፍቅር ራሳችሁን ከገፁ ማግለል ትችላላችሁ” ብሏቸዋል። አባባሉ ግን ጥያቄ ያስነሳል። ለምሳሌ፣ መብትን በፍቅር ስለ መያዝ ምን ይነግረናል? መብት ዕንቅፋት ሲሆንስ? ( 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡9 ) በቀደመው ጥሪ ጸንቶ ማገልገል እንዴት ይቻላል? ( 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፤ ራእይ 2፡4፣5 ) ከስደት ዘመን ይልቅ በ “ሰላምና ነጻነት” ዘመን እነዚህን ጥያቄዎች መጠየቅ ግድ ነው። ደረጀ ፈር ቀዳጅ ነው፤ ዓይነተኛ ነው። ይህን በተለየ መንገድ የተረዳሁት ያሳተማቸውን ዘጠኝ አልበሞች በቅደም ተከተል ደርድሬ ለሰዓታት ባዳመጥኩ ጊዜ ነው። ረጅም “የክርስቲያን ጒዞ” እንደ መጓዝ ነው። ከርቀት ኮረብታን እንደ ማየት፣ አልፎ ወደ ኋላ መመልከት። ለምለም ሣር፣ ወንዝ፣ ቀጥሎ ምድረበዳ። ደስታ፣ ግራ መጋባት፤ የጠራ ሰማይ፣ የፀሐይ ሐሩር፣ ዶፍ፣ ነፋስ፣ ጠ...

እንደሚወራው አይደለም

Image
እንደሚወራው አይደለም የዛሬ ሁለት ዓመት ቢል ጌትስ ኢትዮጵያን በጎበኘበት ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የተነሡት ፎቶ ነው። ከበስተ ኋላቸው የሚታየው የስንዴ እርሻ ነው። ቢል ጌትስ በጣም ሃብታም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ በእርዳታ ስም የዓለም የሥልጣን ማዕከሎችን ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ሰው ነው። በጎ አድራጊ አይደለም ለማለት አይደለም። በጎ በማድረግ ውስጥ ግን ዓለምን በአምሳሉ መጠፍጠፍ ይዟል። አፍሪካውያን በብዛት ስለሚዋለዱ፣ ፈልሰው የአውሮጳን ደም እንዳይከልሱ ያለ ግለ ሰብ ነው። "አላስፈላጊ" ውርጃና ፅንስን መቆለፍን ይደግፋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማድረግ የተቻለው ሰው ነው። የእኛው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ያለ ቢል ጌትስ እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት ዲሬክተር መሆን ቀርቶ ደጁን አይረግጥም ነበር።  ህንዷ ሳይንቲስት ዶ/ር ቫንዳና ሺቫ፣ ስለ ጌትስ የሚገርም አሳብ የሠነዘረችበትን ለማዳመጥ ሊንኩን እዚህ ተመልከቱ። ትንሽ ሰጥቶ ገፈፋ ነው ብላለች። ለመሆኑ ጌትስ እና ዐቢይ ማንም አጠገባቸው ሳይኖር ምን ተባብለው ይሆን? ይህን አጣርቶ የሚነግረን አለ? ዐቢይ ማጋነን ስለሚያበዙ ቃላቸውን መተማመን ከቶ አይቻልም።  ጌትስ፣ በ2002 ዓም መለስ ዜናዊ ጋ መጥቶ፣ "ጂ ኤም ዖ" ስንዴ ድርቅና ረሓብ ላጠቃቸው አገሮች (እንደ ኢትዮጵያ ላሉት) ትልቅ ምርት ያስገኛል የሚል ሸቀጥ አራግፎ ነበር። 2,400 ገበሬዎች 100,000 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዝራት ጀምረው ነበር። አሳቡ ከጌትስ ነው፣ መሞከሪያው አፈሩ የኛ ነው። ዐቢይ፣ ስንዴ ከውጭ ማምጣት ትተን ውጭ አገር መላክ ጀምረናል ባሉን ወቅት፣ ስንት ሺህ ቶን ስንዴ ጂቡቲ ላይ እየተራገፈ ነበር። ያመረትነው ስንዴ ኮታው በጣም ከፍ ማለቱ እውነት ነው...

Ancient Origins of the Ethiopian Calendar

Image
Why Ethiopia Has Its Own Calendar: The Ancient Origins of the Ethiopian Calendar Girma A Demeke (PhD), Research & Publication Director, Institute of Semitic Studies Ethiopia will soon celebrate its New Year, marking a calendar transition distinct from the internationally adopted Gregorian system. This divergence includes both the method of calculating years and the fundamental structure of the day Specifically, from September 11/12 to 31 December, the Ethiopian calendar trails the Gregorian calendar by seven years, and by eight years from 1 January to September 10/11.  Additionally, while the Gregorian day commences at midnight, the Ethiopian day begins at dawn.  Explanations regarding the origins of these differences are often incomplete or convoluted by religious dogma, leaving the underlying mechanics poorly understood. A decade ago, we addressed this topic extensively in a book published in Amharic:  Girma A. Demeke. 2016. The Ethiopian Calendar (Text in Amhari...