እንደሚወራው አይደለም

እንደሚወራው አይደለም

የዛሬ ሁለት ዓመት ቢል ጌትስ ኢትዮጵያን በጎበኘበት ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የተነሡት ፎቶ ነው። ከበስተ ኋላቸው የሚታየው የስንዴ እርሻ ነው። ቢል ጌትስ በጣም ሃብታም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ በእርዳታ ስም የዓለም የሥልጣን ማዕከሎችን ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ሰው ነው። በጎ አድራጊ አይደለም ለማለት አይደለም። በጎ በማድረግ ውስጥ ግን ዓለምን በአምሳሉ መጠፍጠፍ ይዟል። አፍሪካውያን በብዛት ስለሚዋለዱ፣ ፈልሰው የአውሮጳን ደም እንዳይከልሱ ያለ ግለ ሰብ ነው። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማድረግ የተቻለው ሰው ነው። የእኛው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ያለ ቢል ጌትስ እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት ዲሬክተር መሆን ቀርቶ ደጁን አይረግጥም ነበር። 

ህንዷ ሳይንቲስት ዶ/ር ቫንዳና ሺቫ፣ ስለ ጌትስ የሚገርም አሳብ የሠነዘረችበትን ለማዳመጥ ሊንኩን እዚህ ተመልከቱ። ትንሽ ሰጥቶ ገፈፋ ነው ብላለች። ለመሆኑ ጌትስ እና ዐቢይ ማንም አጠገባቸው ሳይኖር ምን ተባብለው ይሆን? ይህን አጣርቶ የሚነግረን አለ? ዐቢይ ማጋነን ስለሚያበዙ ቃላቸውን መተማመን ከቶ አይቻልም። 

ጌትስ፣ በ2002 ዓም መለስ ዜናዊ ጋ መጥቶ፣ "ጂ ኤም ዖ" ስንዴ ድርቅና ረሓብ ላጠቃቸው አገሮች (እንደ ኢትዮጵያ ላሉት) ትልቅ ምርት ያስገኛል የሚል ሸቀጥ አራግፎ ነበር። 2,400 ገበሬዎች 100,000 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዝራት ጀምረው ነበር። አሳቡ ከጌትስ ነው፣ መሞከሪያው መሬት ከኛ ነው። ያገሬ ገበሬ ከፈለገ አፈር ይብላ። ጌትስ፣ ሞንሳንቶ ከተባለ ድርጅት ጋር የንግድ ሽርክና አለው። 

አገራችን አንድ ሃብቷ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር ባደላትና ምስኪን ገበሬዎቿ ያከማቹት የእርሻ ጥበብና ልዩ ልዩ የአዝርእት ዘር ነው። ባለፉት ዓመታት ከመሪዎቻችን አለማስተዋልና ዝርክርክነት የተነሳ ሆላንድ አገር የጤፍን ጠቀሜታ በንግድ ባለቤትነት ለመቆጣጠር ሞክረው ነበር። ከዓለም ዙሪያ ቡና ገዝቶ ቆልቶ በመሸጥ ሃብት ያፈራው የአሜሪካው ስታርበክስ፣ በ1999 ዓም፣ የአገራችንን ሲዳሞና ሐረር ቡና የንግድ ባለቤትነት (trademark) ቋምጦ ነበር፤ ከሸፈበት እንጂ። 

ዐቢይ እና ጌትስ የለበሱት ኮትና ሱሪ መመሳሰሉ ምን ይነግረን ይሆን? ዐቢይ፣ ጌትስ እጅ ላይ ስንት ፍሬ ስንዴ ቆጥረውለት ይሆን? ስንዴይቱን ኪሱ ከትቶ ከአገር ወጣ ወይስ ተፈትሾ?


Comments

Popular posts from this blog

HaileSelassie's Band of Armenian Orphans

The Prince and the last Maharaja

Home of the Shy, Land of the Brave